በቃሊቲ እስር ቤት አካባቢ ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ ማምሻውን እየተሰማ እንደሆነ የአምባ ዲጂታል ምንጮች ጠቁመዋል። ተኩሱ ከምሽት 2፡30 ጀምሮ ሲሰማ እንደነበር ታውቋል።
በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ጃዋር ሙሐመድ፣ በቀል ገርባ፣ እስክንድር ነጋን የመሳሰሉ የፖለቲካ እስረኞች መኖራቸው ይታወቃል።
ምሽቱን መቐለ በሕወሓት ታጣቂዎች እጅ መውደቋን ተከትሎ፣ በአዲስ አበባ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የፌዴራል ፖሊስና ጸጥታ አስከባሪዎች በጎዳናዎች ላይ የሚታዩ ሲሆን፣ ጥበቃ መጠናከሩንም የአይን እማኞች ተናግረዋል።