ያለፉትን ሦስት ዓመታት የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎትን በዋና ሥራ አስፈጻሚ የመሩት ሐና አርዓያሥላሴ ቀድሞ በምክትል ኮሚሽነርነት የሠሩበትን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በኮሚሽነርነት ለመምራት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ተሾመዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ሐና አርኣያሥላሴን ለኮሚሽኑ ኮሚሽነርነት የሾሙት ከትላንት ረቡዕ ጥር 8፣ 2016 ጀምሮ ነው፡፡
ሐና ከአሜሪካው ኒውዮርክ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት በህግ ንድፈ ሃሳብ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ይዘዋል፡፡ ኮሚሽነሯ ወደዚህ ኃላፊነት ቦታ ከመምጣታቸው አስቀድሞ፤ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ምክትል ስራ አስፈጻሚነት በጠቻመሪ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤትም ሠርተዋል።