አምባ ዲጂታል፣ ማክሰኞ ነሐሴ 4፣ 2013 ― የደሴ ከተማ አስደዳደር ባወጣው መግለጫ በሰዐት የተገደበ የተሽከርካሪ እና የሰው እንቅስቃሴ ገደብ መጣሉን አስታውቋል።
ገደቡ የተጣለው ለከተማው ህዝብ ሁለንተናዊ ደህንነት መሆኑን አስተዳደሩ ገልጿል።
በዚህም መሠረት ለከተማዋ ነዋሪዎች ከምሽቱ 2 ሰአት ጀምሮ ከተፈቀደላቸው የፀጥታ አካላት ውጭ የትኛውም ዓይነት እንቅስቃሴ ተከልክሏል።
ከተፈቀደላቸው የፀጥታ ተቋማትና የጤና ተቋማት ተሽከርካሪዎች ውጪ ከምሽቱ 2:00 ጀምሮ እንቅስቃሴ እንዲገደብ ተወስኗል።
የሶስት እግር ባጃጅ ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ እስከ ምሽቱ 12:00 ብቻ እንዲሆን መወሰኑን የከተማዋ አስተዳደር አስታውቋል።
ውሳኔው ከዛሬ ነሀሴ 4፣ 2013 ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግም ያስታወቀ ሲሆን የከተማው ነዋሪዎች ትብብር እንዲያደርጉ የከተማዋ ኮምኒኬሽን ጉዳዮች በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስፍሯል።