Thursday, October 10, 2024
spot_img

በኦሮሚያ ክልል በግጭት ሳቢያ የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር 55 ሺሕ መድረሱ ተነገረ

አምባ ዲጂታል፣ ሐሙስ ሰኔ 3፣ 2013 ― በክልሉ በግጭት ሳቢያ 9 ሺሕ አባወራዎች ወይም 55 ሺሕ 163 ሰዎች መፈናቀላቸውን የምሥራቅ ወለጋ ዞን የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል፡፡

በክልሉ ለተፈናቃዮቹ ቁጥር ማሻቀብ በቅርቡ የምሥራቅ ወለጋ ዞኖች በሆኑት በሊሙ እና ሐሮ ሊሙ ወረዳዎች እንዲሁም በቤንሻጉል ጉሙዝ ከማሼ ዞን ያሶ እና ሶጌ ወረዳዎች የነበረው አለመረጋጋት ምክንያት ነው መባሉን አዲስ ስታንዳርድ አስነብቧል፡፡

በተለይ በወለጋ ዞኖች የታጠቁ ኃይሎች መኖራቸው የጸጥታ ሁኔታውን ተለዋዋጭ ማድረጉንና ይህም የሰዎች መፈናቀል እና ሕይወት መጥፋት ማስከተሉን የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ እርዳታ ማስተባበሪያ ቢሮ መግለጹንም ዘገባው አስታውሷል፡፡

በቄለም ወለጋ እና ምዕራብ ወለጋ ዞኖችም ጥቂት ቀናት የቀሩትን ምርጫ በማስመልከት በሦስት እግር ተሸከርካሮች ላይ የሰአት እላፊ ገደብ እንደተጣለም ተነግሯል፡፡

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትኩስ ርዕስ

- Advertisment -spot_img