Sunday, September 22, 2024
spot_img

በትግራይ ግጭት ወድመው የነበሩ እና አዳዲስ የሕክምና ቁሳቁስ አቅርቦቶችን ያገኙ አንዳንድ የጤና ተቋማት ዳግመኛ ተዘርፈዋል ተባለ

አምባ ዲጂታል፣ ሐሙስ ሰኔ 24፣ 2013 ― በትግራይ ግጭት ወድመው የነበሩ እና አዳዲስ የሕክምና ቁሳቁስ አቅርቦቶችን ያገኙ አንዳንድ የጤና ተቋማት ዳግመኛ መዘረፋቸውን ዓለም አቀፉ ድንበር የለሽ የሐኪሞች ድርጅት አስታውቋል።

የሐኪሞች ቡድኑ የጤና ተቋሚቱ በማን እና እንዴት እንደተዘረፉ ያለው ነገር የለም።

የድንበር የለሽ የሐኪሞች ድርጅት የአስቸኳይ ጊዜ ፕሮግራም ሥራ አስኪያጅ ማሪ ካርመን ቪዮለስ እንዳሉት፣ በትግራይ ክልል ከ 75 በመቶ በላይ የህክምና ተቋማት ወድመዋል ወይም ተዘርፈዋል እንዲሁም በክልሉ 5.5 ሚሊዮን ሰዎች ለአስቸኳይ የምግብ ዋስትና ተጋልጠዋል።

ዓለም አቀፉ የድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን ከሳምንት በፊት ባልደረቦቹ ትግራይ ውስጥ «በጭካኔያዊ ሁኔታ ተገድለው» መገኘታቸውን ማሳወቁ አይዘነጋም።

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትኩስ ርዕስ

- Advertisment -spot_img