Sunday, September 22, 2024
spot_img

ደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች ከአብዬ ግዛት መውጣታቸውን እንደማትቀበል አስታወቀች

አምባ ዲጂታል፣ ቅዳሜ መስከረም 8፣ 2014 ― የደቡብ ሱዳን መንግስት በአብዬ ግዛት በሰላም ማስከበር ስራ ላይ የተሰማሩ የኢትዮጵያ ወታደሮች እንዲወጡ ሱዳን ያቀረበችውን ጥያቄ ውድቅ አደረጓል።

የተባበሩት መንግስታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ረዳት ሚኒስትር ዣን ፒዬር ላክሮይክስ ባለፈው ሳምንት ደቡብ ሱዳንን መጎብኘታቸውን ተከትሎ መግለጫ ሰጥተዋል።

ሱዳን ፖስት እንደዘገበው የደቡብ ሱዳን የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስቴር በተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ልዑክ እና በከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እንዲሁም በፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት በአብዬ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪዎች ሁኔታ ላይ ያተኮረ ውይይት አድርገዋል፡፡

የደቡብ ሱዳን መንግስት በመግለጫው በአወዛጋቢው ክልል ውስጥ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ኃይልን ለመተካት ሱዳን ያቀረበችውን ጥሪ ውድቅ ማድረጉን አስታውቋል።

የአገሪቱ መግለጫ ‹‹በዚህ ሁኔታ የደቡብ ሱዳን ሪፐብሊክ ይህ ኃይሉ የተሰጠውን ተልዕኮ በሙያ እና በገለልተኝነት እያከናወነ ባለበት ወቅት የኢትዮጵያ ጦር እንዲወጣ በሚደረገው ጥሪ እንደማይስማማ ለመግለፅ እንወዳለን›› ብሏል፡፡

የደቡብ ሱዳን መንግሥት የአብይን ግዛት ለመጨረሻ ጊዜ እልባት እንዲያገኝ ፓለቲካዊ ሂደት እንዲጀመር ጥሪውን በድጋሚ አቅርቧል፡፡

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትኩስ ርዕስ

- Advertisment -spot_img