አምባ ዲጂታል፣ ሐሙስ ነሐሴ 27፣ 2013 ― በትግራይ ክልል ጦርነቱ ከጀመረ አንስቶ መገደላቸው ይፋ ከተደረጉ 12 የረድኤት ሠራተኞች ተጨማሪ 11 ሌሎች መገደላቸውን ተከትሎ የሟቾቹ ቁጥር 23 መድረሱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታውቋል፡፡
ድርጅቱ ተገድለዋል ያላቸው ተጨማሪ 11 የረድኤት ሠራተኞች በክልሉ የሚነቀሳቀሰው የማህበረ ረድኤት ትግራይ ባልደረቦች ናቸው፡፡
የግድያውን ይፋ መደረግ ተከትሎ የተናገሩት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ ቢሮ የሰብአዊ ጉዳዮች አስተባባሪ የሆኑት ግራንት ሊያቲ ግድያው ኮንነዋል፡፡
በትግራይ ክልል በተመሳሳይ ባሳለፍነው ሰኔ ወር የድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን ባልደረባ የሆኑ ሦስት ሰዎች መገደላቸው መነገሩ ይታወሳል፡፡