አምባ ዲጂታል፣ ሐሙስ ነሐሴ 20፣ 2013 ― የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።
ፕሬዝዳንቱ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ ተቀብለዋቸዋል።
በዚሁ የአቀባበል ሥነስርአት ላይም የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል፣ የመከላከያ ሚኒስትር ዶ/ር ቀንአ ያደታ እንዲሁም የተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ተገኝተዋል።
ፕሬዝዳንቱ በኢትዮጵያ ቆይታቸው በሁለትዮሽ ጉዳዮች ከተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ጋር እንደሚመክሩ እንደሚጠበቅ የመንግስት ሚዲያዎች ዘግበዋል፡፡