Wednesday, October 16, 2024
spot_img

በአዳማ እና ቢሾፍቱ ሕወሃት እና ‹‹ሸኔ›› የሚባለውን ቡድን የሚወግዝ ሰልፍ እየተካሄደ ነው

አምባ ዲጂታል፣ ረቡዕ ነሐሴ 12፣ 2013 ― በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት የተፈረጁትን ሕወሃት እና መንግስት ‹‹ሸኔ›› የሚለውና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት በሚል የሚጠራውን ቡድን የሚያወግዝ ሰልፍ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ስለመሆኑ የመንግስት ሚዲያዎች ዘገባ ያመለክታል፡፡

በተቃውሞ ሰልፉ ላይ ‹‹ሸኔ እና ህወሃት የኢትዮጵያ ህዝብ ታሪካዊ ጠላቶች ናቸው››፣ ‹‹ለኢትዮጵያ ሰላምና አንድነት ዘብ እንቆማለን›› የሚሉና ቡድኖቹን የሚያወግዙ መፈክሮች መስተጋባታቸው ተመላክቷል፡፡

በተመሳሳይ የቢሾፍቱ ከተማ ነዋሪዎችም ህወሃት እና ሸኔ የሽብር ቡድኖችን የሚያወግዝ ሰልፍ እያደረጉ እንደሚገኙ የሚያመለክቱ የፎ መረጃዎች ወጥተዋል፡፡

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትኩስ ርዕስ

- Advertisment -spot_img