የሕዳሴ ግድብ 2 ተርባይኖች ለማንቀሳቀስ የሚያስፈልገውን የውሃ መጠን መሙላቱ ታወቀ።
የሕዳሴ ግድብ ዛሬ የሁለተኛውን አመት የህዳሴ ግድብ ሙሌት ተገባዶ ውሃው በግድቡ አናት ላይ መፍሰሱን መንግስት አስታውቋል።
ይህ ማለት 2 ተርባይኖችን ለማንቀሳቀስ የሚያስፈልገውን የውሃ መጠን እንደያዘ ነው የተነገረው።
እዚህ ደረጃ ለመድረስ በዘንድሮው አመት መጠነ ሰፊ ስራ ሰርተናል ያለው መንግስት፣ በቀጣይ ሁለቱ ተርባይኖች እንዲያመነጩ ብርቱ ስራዎች እየተሰሩ ነው እናም ያንን በቅርብ ወራት በማጠናቀቅ ልፋታችንን ውጤት ላይ እናደርሳለን ሲል አክሏል።