Update: በአቶ አራርሶ ቢቂላ የሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር “በኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስና በኦሮሞ ነጻነት ግንባር ስም እየተሰራጨ ነው” ያለውን “የሽግግር መንግስት” አዋጅ እንደማይቀበል ገልጿል።
ፓርቲው ባወጣው መግለጫው በአቶ ዳውድ ኢብሳ በሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ይፋዊ ገፅ የወጣውን የሽግግር መንግስት ምክረ ሀሳብ ጥሪ ነቅፎ አቋሙን ገልጾበታል፡፡
የፓርቲው ባለስልጣናት በሰጡት ተጨማሪ ማብራሪያም ፓርቲያቸው ስልጣን በምርጫ እንዲተላለፍ ያምናል ማለታቸውንም ዶይቼ ቬለ ዘግቧል።