በትግራይ ክልል ውስጥ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ልጆቻቸውን የሚያስተምሩት ወላጆች ወደ ቤተመንግሥት እያመሩ ይገኛሉ ተብሏል። የተማሪዎቹ ወላጆች ዛሬ ማለዳ አዲስ አበባ በሚገኘው የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ቢሮ በማምራት የልጆቻቸውን ቀጣይ እጣ ፋንታ ጠይቀዋል፡፡
ከቢሮው አጥጋቢ ምላሽ ባለማግኘታቸው ወደ ኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ያመሩት ቅሬታ አቅራቢዎቹ በአሁን ሰዓት ወደ ቤተመንግስት እያመሩ ይገኛሉ መባሉን አዲስ ዘይቤ ዘግቧል።
የተጓዦቹ የመንግሥትን ይሁንታ ለማግኘት ወደ ቤተመንግሥት እያመሩ የሚገኙት ከተቻለ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድን ካልሆነም የሚመለከተውን አካል አግኝተው ለጥያቄአቸው ምላሽ ለማግኘት ነው፡፡