Saturday, October 12, 2024
spot_img

ሕብር ኢትዮጵያ የምርጫ ታዛቢ እንደተገደለበት አሳወቀ

አምባ ዲጂታል፣ ሐሙስ ሰኔ 17፣ 2013 ― ሕብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በደቡብ ኦሞ ዞን ሐመር ወረዳ ጊመካ ቀበሌ ነዋሪ የነበረ የፓርቲው አባል እና የምርጫ ታዛቢ የነበሩት አቶ ግርማ ታደሰ ተደብድበው እንደተገደሉበት አሳውቋል፡፡

ፓርቲው፣ አባሉ እና የምርጫው ታዛቢው የነበሩት የአቶ ግርማ ታደሰ ገዳዮች ማንነት ለጊዜው ማንነታቸው አለመታወቁን ነው የገለጸው፡፡ ጉዳዮን ለሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት አሳውቆ ‹‹ምርመራ እየተካሔደ›› ነው ያለው ሕብር ኢትዮጵያ፣ በአባሉ ግድያ ሐዘኑን ገልጧል፡፡

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትኩስ ርዕስ

- Advertisment -spot_img