ብልፅግና እጩ ባላቀረበበት ምርጫ ክልል 28 መራጮች ድምጽ እየሰጡ ነው።
ብልፅግና እጩ ባላቀረበበት በአዲስ አበባ ከተማ ምርጫ ክልል 28 መራጮች ድምፅ እየሰጡ ነው።
በዚህ ክልል በግል የሚወዳደሩትን ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ጨምሮ 10 እጩዎች ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ይወዳደራሉ።
በአዲስ አበባ አንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች ምርጫው በሠላማዊ መንገድ አየተካሄደ ቢሆንም፣ ምርጫው ዘግይቶ መጀመር፣ የቅንጅት ጉድለት እንዲሁም የምርጫ ወረቀት አለመሟላት የመሰሉ እንከኖች ማስተዋላቸውን መራጮች እየተናገሩ እንደሚገኙ የሚወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡
የፎቶ ምንጭ፡ አሻም ቲቪ