Friday, October 11, 2024
spot_img

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ ጥሪ አቀረቡ

አምባ ዲጂታል፣ ሐሙስ ሰኔ 10፣ 2013 ― የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዛሬ በሰጠው መግለጫ በመጪው ሰኞ የሚካሄደው አገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ጥሪ አቅርበዋል።

ጉባኤው ስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ ብዙ አሳሳቢ ጉዳዮች ባሉበት የሚካሄድ በመሆኑ ሁሉም አካላት ጠብ አጫሪ ከሆኑ ድርጊቶችና ንግግሮች እንዲቆጠቡና ምርጫው ሰላማዊ እንዲሆን ኢትዮጵያውያን በተለይ ወጣቱ የበኩሉን እንዲወጣ አሳስቧል፡፡

የምርጫው ውጤት በሚመለከተው አካል እስኪገለጽ ድረስ፣ ሁሉም በትዕግስት ሊጠባበቅ እንደሚገባም ገልጸዋል።

ምርጫውን የሚያስተባብሩ አካላትም የምርጫውን ሂደት በፍጹም ግልጸኝነት እንድያስተባብሩ ጥሪ ማቅረባቸውን የመንግሥት ሚዲያዎች ዘግበዋል፡፡

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትኩስ ርዕስ

- Advertisment -spot_img