አምባ ዲጂታል፣ ማክሰኞ ሰኔ 8፣ 2013 ― የፊታችን ሰኞ ሰኔ 14፣ 2013 ለሚካሄደው አገር አቀፉ ምርጫ ሁሉም የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ዝግ እንደሚሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አሳውቀዋል፡፡ የእለቱን ዝግ መሆን ለማካካስ በሚመጣው ቀጥሎ በሚመጣው ቅዳሜ ወደ ሥራ እንደሚገባ ነው የገለጹት፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስሰር ገጻቸው ላይ ሰኔ 14 ሁለት ነገር እንትከል፤ በእጃችን ችግኞችን፣ በካርዳችን ዴሞክራሲን የሚል መልእክት አስተላልፈዋል፡፡