Thursday, October 10, 2024
spot_img

መንግሥትና የአገሪቱ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች መጪውን ምርጫ ውጥረቶችን ለማርገብ እንዲጠቀሙበት ተጠየቀ

አምባ ዲጂታል፣ ረቡዕ ሰኔ 2፣ 2013 ― መንግሥትና የዴሞክራሲ ኃይሎች ከቀናት በኋላ የሚካሄደውን ምርጫ ውጥረቶችን ለማርገብ እንዲጠቀሙበት በአውሮፓ ኅብረት ፓርላማ የሰብአዊ መብቶች ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ ማሪያ አሬና ጠይቀዋል።

በአውሮፓ ፓርላማ ላይ በተነበበው መግለጫቸው በአገሪቱ የቀጠለው ብሔር ተኮር ግጭት እጅጉን እንደሚያሳስባቸው የገለጹት ማሪያ አሬና፣ የኢትዮጵያውያን ስቃይ ሊገታ እንደሚገባም ነው ያመለከቱት።

መንግስትም የዜጎችን ሰብአዊ መብቶች እንዲከበሩ ግዴታ እንዳለበት የገለጹ ሲሆን፣ ተፈናቃዮች ባሉባቸው አካባቢዎችም ያልተገደበ የሰብአዊ አቅርቦት እንዲኖር ማድረግ አለበት ነው ያሉት።

የአውሮፓ ኅብረት ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ የኢትዮጵያ መንግሥት የዜጎችን የሰብአዊ መብቶች እንዲጠብቅና ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች ለተፈናቀሉ ያልተገደበ ሰብአዊ አቅርቦት እንዲኖር መጠየቁ የሚታወስ ነው።

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትኩስ ርዕስ

- Advertisment -spot_img