Thursday, October 10, 2024
spot_img

የግብፅ የውጭ ጉዳይ እና የውሃና መስኖ ሚኒስትሮች ካርቱም ገቡ

አምባ ዲጂታል፣ ረቡዕ ሰኔ 2፣ 2013 ― የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሹክሪ እና የውሃ ሀብትና መስኖ ሚኒስትር ሞሐመድ አብደል አቲ ከሱዳን ባለስልጣናት ጋር ለመመካር ካርቱም ገብተዋል።

አል ዐይን ኒውስ እንደዘገበው ሚኒስትሮቹ ካርቱም ሲደርሱ የሱዳን የውጭ ጉዳይ እና የውሃና መስኖ ሚኒስትሮች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በካርቱም በሚኖራቸው ቆይታም ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ እየገነባች ባለው የሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ትኩረት አድርገው ይመክራሉ ነው ተባለው።

ሚኒስትሮቹ በካርቱም ቆይታቸው ከሱዳን ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌተናል ጄኔራል አብደል ፈታህ አል-ቡርሃን እና ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብደላ ሀምዶክ ጋር እንደሚመክሩም ተነግሯል።

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትኩስ ርዕስ

- Advertisment -spot_img