Thursday, October 10, 2024
spot_img

በትግራይ ሰዎች በረሃብ እየሞቱ እንደሚገኙ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዳይሬክተር ገለጹ

አምባ ዲጂታል፣ ረቡዕ ሰኔ 2፣ 2013 ― በትግራይ ክልል ሰዎች በረሃብ ምክንያት ሕይወታቸው እያለፈ እንደሚገኝ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዳይሬክተር ዴቪድ ቤስሊይ በትዊተር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል፡፡

ዳይሬክተሩ በትግራይ ጉዳይ ጊዜው እያለቀ ነው ያሉ ሲሆን፣ አሁንም ቢሆን በክልሉ ያልተገደበ የሰብአዊ አቅርቦት እንዲዳረስ ሁሉም አካላት ቁረጠኝነት ሊያሳዩ እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት፡፡ 

በተመሳሳይ ከሁለት ቀናት በፊት በትግራይ ክልል በርካታ አካባቢዎች በረሃብ አፋፍ ላይ መሆናቸው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ዋና ጸሐፊ አንቶንዮ ጉተሬዝ መናገራቸው የሚታወስ ነው፡፡

ዋና ጸሐፊው በክልሉ ‹‹አሁን የሚከናወኑ ተግባራት ለበርካታ ሰዎች የመኖርና አለመኖር ጉዳይ መሆናቸውን መረዳት ተገቢ ነው›› ሲሉም ገልጸው ነበር፡፡

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትኩስ ርዕስ

- Advertisment -spot_img