አምባ ዲጂታል፣ ረቡዕ ግንቦት 25፣ 2013 ― ዘምዘም ባንክ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ከወለድ ነጻ ባንክ በመሆን አገልግሎት መጀመሩን አስታውቋል፡፡
ባንኩ የሸሪአን መርህን መሰረት ባደረገ መልኩ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን፣ አገልግሎቱንም የሚሰጡት በባንክ ዘርፍ የዳበረ ልምድ ያላቸው ስመጥር ባለሞያዎች እንደሚሰጥ ነው የገለጸው፡፡
ባንኩ በነገው እለት የመክፈቻ ስነ ስርአቱን ያካሄዳል ተብሎ ተጠብቋል፡፡