አምባ ዲጂታል፣ ሰኞ ግንቦት 23፣ 2013 ― ከቀናት በፊት አገራቸው አሜሪካ በኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ላይ የጣለችውን የቪዛ ማዕቀብ የተቃወሙት ሴናተር ጂም ኢንሆፌን በዛሬው እለት ኢትዮጵያ ተገኝተዋል፡፡
የሴናተር ጂም ኢንሆፌን ያሳወቁት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ‹‹ጂም ኢንሆፌን ወደ ሁለተኛው ቤትዎ ኢትዮጵያ እንኳን ደኅና መጡ እላለሁ›› ሲሉ በፌስቡክ ገጻቸው ላይ አስፍረዋል፡፡
የአሜሪካዋ ኦክላሆማ ግዛት ሴናተር የሆኑት ጂም ኢንሆፍ የባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ላይ የጣለውን የቪዛ ክልከላ በተቃወሙበት ወቅት ኢትዮጵያ የአሜሪካ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋት ገልጸው ነበር፡፡