አምባ ዲጂታል፣ ረቡዕ ግንቦት 18፣ 2013 ― ከአማራ ክልል እና ከሱዳን የተመለሱ 2 ሺሕ ሰዎችን በምዕራብ ትግራይ ዳንሻ አካባቢ ለማስፈር ዝግጅት መደረጉ ተነግሯል።
ከነዚህ 2 ሺሕ ሰዎች ተጨማሪ በአካባቢው በዚህ ዙር በአጠቃላይ 6 ሺሕ ሰዎች ይሰፍራሉ ተብሏል።
በጥቅምት የመጨረሻ ሳምንት በፌደራል መንግሥት እና በሕወሃት መካከል የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል ቀድሞ ውዝግብ የነበረባቸውን የምዕራብ ትግራይ አካባቢዎችን መያዙ መነገሩ ይታወሳል።