Tuesday, October 8, 2024
spot_img

አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን መንግሥት ከሕወሃት ጋር እንዲደራደር ጠይቀው እንደነበር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ

አምባ ዲጂታል፣ ሐሙስ ግንቦት 12፣ 2013 ― በቅርቡ ኢትዮጵያን ጨምሮ በኤርትራ፣ ሱዳን እና ግብጽ ጉብኝት ያደረጉት የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን ‹‹ከሕወሓት ጋር ተነጋገሩ የሚል›› ሐሳብ አንስተው እንደነበር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በዛሬው እለት በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል፡፡

ቃል አቀባዩ በመግለጫቸው ከዚህ በተጨማሪ በምርጫ ጉዳይ ላይም ጄፍሪ ፌልትማን ሐሳብ ሰንዝረው እንደነበር ያስታወሱ ሲሆን፣ ከምርጫው ጋር በተገናኘ ‹‹ምርጫ አታካሂዱ አንልም፤ የአሜሪካ መንግሥትም ለዚህ አላከኝም›› ማለታቸውንም አስታውሰዋል።

በሌላ በኩል ከሕዳሴ ግድብ ጋር በተገናኘም ያነሱት አምባሳደር ዲና፣ ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በቅርቡ እንደሚጀመር አስታውቀዋል፡፡

ቃል አቀባዩ የግድቡ ግንባታ 80 በመቶ መጠናቀቁን ያነሱ ሲሆን፣ እስካሁን ለግድቡ ግንባታ 15 ቢሊዮን ብር በሀገር ውስጥ እና በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መዋጣቱን አስታውቀዋል።

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትኩስ ርዕስ

- Advertisment -spot_img