አምባ ዲጂታል፣ እሑድ መስከረም 9፣ 2014 ― የጅቡቲው ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ዑመር ጉሌህ ወደ አገራቸው መመለሳቸውን የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማሕሙድ አሊ ዩሱፍ በትዊተር ገልጸዋል።
ከቀናት በፊት በፀና ታመው በፈረንሳይ አገር ሕክምና ላይ እንደሚገኙ ቢነገርም፣ በአገሩ መንግስት ባለስልጣናት ሕመም ላይ ሳይሆኑ እረፍት ላይ ናቸው የተባለላቸው ጉሌሕ፣ ወደ ጅቡቲ የተመለሱት ዛሬ ከሰዓት መሆኑ ነው የተገለፀው።