የኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬ እለት ሁርሶ ተገኝተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማሠልጠኛው ተገኝተው በመከላከያ የሠላም ማስከበር ማዕከል የሁርሶ ኮንቲንጀንት ማሠልጠኛ ትምህርት ቤት በሦስተኛ ዙር ያሠለጠናቸውን ምልምል የሠራዊት አባላት አስመርቀዋል፡፡ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ተመራቂዎቹ መለዮ እንዲለብሱ መፍቀዳቸውን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ላይ አስነብቧል፡፡