Wednesday, October 9, 2024
spot_img

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ማክስ 8 አውሮፕላኖችን ወደ በረራ ሊመልስ ነው

አምባ ዲጂታል፣ ዐርብ ነሐሴ 28፣ 2013 ― የኢትዮጵያ አየር መንገድ ማክስ 8 ቦይንግ 737 አውሮፕላኖቹን ከቀጣዩ ዓመት ጥር ጀምሮ እንደገና ወደ በረራ ሊመልስ መሆኑ ተነግሯል፡፡

ቦይንግ ኩባንያ በማክስ 8 አውሮፕላን ላይ ያደረጋቸው ማሻሻያዎች፣ የበረራ ደኅንነትን የሚያረጋግጡ እንደሆኑ የአየር መንገዱ ሥራ አስፈጻሚ ተወልደ ገ/ማርያም ተናግረዋል።

አየር መንገዱ አውሮፕላኖቹን እንደገና ለማብረር የወሰነው፣ ከ2 ዓመት በፊት ለተከሰከሰበት ማክስ 8 አውሮፕላኑ ከቦይንግ ኩባንያ ከፍርድ ቤት ውጭ የካሳ ክፍያ ለማግኘት መስማማቱን ተከትሎ ነው።

አየር መንገዱ በአዲስ አበባ የተለያዩ የአውሮፕላን መገጣጠሚያዎችን ለማምረት የሚያስችለውን ስምምነት ከሰሞኑ ከቦይንግ ኩባንያ ጋር ስምምነት መፈጸሙ መነገሩ አይዘነጋም፡፡

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትኩስ ርዕስ

- Advertisment -spot_img