አምባ ዲጂታል፣ ሰኞ ሐምሌ 12፣ 2013 ― ከብሔራዊ ቴአትር ፊት ለፊት የሚገኘው ዕድሜ ጠገቡ በጎ አድራጎት ሕንጻ ሊፈርስ መሆኑ ተሰምቷል።
በተመሳሳይ ከበጎ አድራጎት አጠገብ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሆቴል ከስድስት ዓመታት ውዝግብ በኋላ ሊፈርስ መሆኑም ተነግሯል።
ሁለቱ ሕንጻዎች ከተገነቡ 80 ዓመታት ያለፋቸው ሲሆን፣ ቦታው ታዋቂው ባለሐብት በላይነህ ክንዴ ለሚያስገነቡት ሰማይ ጠቀስ ሆቴል ግንባታ ይውላል መባሉን ፎርቹን ጋዜጣ አስነብቧል።
በጎ አድራጎት ሕንጻ በውስጡ ላየን ባር እንዲሁም ታዋቂውን ሺ ሰለሞን ሱፐር ማርኬት ይዞ የነበረ ሲሆን፣ ከስድስት ዓመታት ውዝግብ በኋላ ቦታው ሊፈርስ በመሆኑ ሁለቱም ከጥቂት ሳምንታት በፊት ለቀው ወጥተዋል።