Monday, October 14, 2024
spot_img

እነ ስብሐት ነጋ ላይ በዚህ ሳምንት ክስ እንደሚመሠረት ዐቃቤ ሕግ አሳወቀ

አምባ ዲጂታል፣ ማክሰኞ ሐምሌ 6፣ 2013 ― በሕግ አግባብና በፍትሕ መንገድ ላይ ሳይሆን በሌሎች ግፊቶች ነጻ ለመውጣት ሲጣጣሩ ነበሩ የተባሉ ስብሐት ነጋን ጨምሮ 42 ተጠርጣሪ በሽብርተኝነት የተፈረጀው ሕወሓት አባላት ላይ በዚህ ሳምንት ክስ እንደሚመሰረትባቸው ምክትል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አቶ ፈቃዱ ፀጋዬ አስታውቀዋል፡፡

ምክትል ጠቅላይ አቃቤ ሕጉ ለመንግሥታዊወ ልሳን አዲስ ዘመን እንደገለጹት፣ እነዚህ 42 ተጠርጣሪ የሕወሓት አባላት በቀዳሚ ምርመራና በዋና ምርመራቸው ወቅት ጉዳያቸውን ፖለቲካዊ ይዘት እንዲኖረው ጥረት ሲያደርጉ ነበር፡፡

የተለያዩ ሰበቦችን በመደርደር የፍርድ ሂደቱ ዘገየ ለማስባል መሞከራቸውን ያመለከቱት አቶ ፈቃዱ፣ በሕግ አግባብና በፍትሕ መንገድ ሳይሆን በሌሎች ግፊቶች ነጻ እንወጣለን በሚል ሒሳቦችን ሰርተው ከእስር ለመውጣትም ሲጣጣሩ ቆይተዋል ማለታቸውም ተመላክቷል፡፡

ነገር ግን ምርመራው በጣም ከታሰበው በላይ በፍጥነት በመጠናቀቁ ይህ ስሌታቸው እንዳልሰራ አመልክተዋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በሰሩት ልክ ሕግ ተገቢውን ፍርድ ይሰጣቸዋል ያሉት አቶ ፈቃዱ፤ በቀጣዩ ሳምንት ተጠርጣሪዎቹ ለክስ እንደሚቀርቡ ያመለከቱ ሲሆን፣ ክሱ የወንጀል ክስ በመሆኑም ፍጥነቱ ምን ያህል ተቀናጅቶ እንደተሰራበት የሚያመላክት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትኩስ ርዕስ

- Advertisment -spot_img