Update: በፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተቃውሞ የቀረበበትን የጠ/ሚ ዐቢይ ቃለ ምልልስ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን እንዳይተላለፍ አሳሰበ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለፋና ቴሌቪዥን የሰጡትና በፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተቃውሞ የቀረበበትን ቃለ መጠይቅ በዚህ በጥሞና ወቅት በመገናኛ ብዙሃን እንዳይተላለፍ ሲል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ባለስልጣን ማሳሰቡን ኢዜአ ዘግቧል።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ እድሪስ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ምንም እንኳን ቃለ መጠይቁ የመንግስት የስራ ክንውኖች ላይ ያተኮረና የምርጫ ቅስቀሳ እንዳልሆነ ቢታወቅም በዚህ ጥሞና ወቅት ሊተላለፍ አይገባም ማለታቸውን ዘገባው አመልክቷል።