ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
አንጋፋው የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ሊቅ ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ በ90 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
ፕሮፌሰር ጌታቸው ከ1950 አስከ 1960ዎቹ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሴማዊ ቋንቋ ጥናት፣ በአማርኛ ግዕዝ ሥነ ጽሑፍ እና ሰዋሰው በመምህርነት አገልግለዋል፡፡
በአማርኛ ቋንቋ ከታተሙ ሥራዎቻቸው መካከል ደቂቀ አስጢፋኖስ፣ አንዳፍታ ላውጋችሁ፣ ስለግዕዝ ሥነ-ጹሑፍ የተሰበሰቡ አንዳንድ ማስታወሻዎች፣ ባሕረ ሐሳብ የሚሉት እንደሚገኙበት ኢቢሲ ዘግቧል፡፡