Thursday, October 10, 2024
spot_img

በመቐለ ከ13 ወራት በኋላ ትምህርት ሊጀመር ነው

አምባ ዲጂታል፣ ቅዳሜ ግንቦት 28፣ 2013 ― በትግራይ ክልል መቀመጫ በመቐለ ተማሪዎች ከ13 ወራት አስገዳጅ እረፍት በኋላ ከመጪው ግንቦት ሰኞ 30፣ 2013 ጀምሮ መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደት እንደሚጀምሩ ተገለፀ።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ በመቐለ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲቋረጥ ምክንያት የነበሩት ችግሮች መፍታታቸውን በመግለጽ፣ በሰባቱ ክፍለ ከተሞች በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ከመጪው ሰኞ ጀምሮ ተማሪዎቻቸውን በመቀበል የትምህርት ሂደቱን እንደሚጀምሩ አስታውቋል።

ቢሮው ባለፈው ዓመት በሀገሪቱ ባጋጠመ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ እንዲሁም ዘንድሮ በክልሉ በተፈጠረው የፀጥታ አለመረጋጋት ምክንያት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ርቀው እንደነበር አስታውሷል።

ለዚህም ዛሬና ነገ በከተማው የሐወዝብ ንቅናቄ ተግባራት ይካሄዳል የተባለ ሲሆን፣ በዚህ እንቅስቃሴ የሚመለከታቸው አጋር አካላት በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርቧል ሲል የዘገበው የትግራይ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ ነው፡፡

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትኩስ ርዕስ

- Advertisment -spot_img