አምባ ዲጂታል፣ ረቡዕ ግንቦት 25፣ 2013 ― በትግራይ ክልል ሰብዓዊ ዕርዳታ ማቅረብ እንዲቻል ተኩስ አቁም መደረግ እንዳለበት በአዲስ አበባ የሚገኙ የጀርመን፣ የዩናይትድ ኪንግደም፣ የአሜሪካ እና ፈረንሳይ ኢምባሲዎች በትዊተር ገጾቻቸው ጠይቀዋል፡፡
ኤምባሲዎቹ በክልሉ ተኩስ በአስቸኳይ ይቁም የሚለውን ዓለምአቀፍ ጥሪ እንደሚደግፉ ገልጠዋል። ከሰሞኑ በክል ተኩስ በአስቸኳይ እንዲቆም እየጠየቁ ካሉት ሀገራት መካከል አሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ካናዳ፣ ስዊድን፣ ዴንማርክ እና ኖርዌይ ጭምር ይገኙበታል።