Sunday, October 6, 2024
spot_img

ሰበር ዜና

አምባ ዲጂታል፣ ቅዳሜ ሚያዝያ 23፣ 2013 ― የሚንስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ የሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ሕወሓት) እና “ሸኔ”ን በሽብርተኛ ድርጅትነት እንዲሰየሙ የውሳኔ ሐሳብ ማሳለፉ ተሰምቷል።

ምክር ቤቱ የሽብር ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በወጣው ዐዋጅ ቁጥር 1176/2012 አንቀጽ 18 እና 19 መሠረት “ሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ሕወሓት)” እና “ሸኔ” የሽብር ወንጀልን ዓላማቸው አድርገው የሚንቀሳቀሱ በመሆኑና የድርጅቶቹ የሥራ አመራር ወይም ወሳኔ ሰጭ አካላት ወንጀሉን አምነው የተቀበሉት ወይም አፈጻጸሙን እየመሩት በመሆኑ፤ የሽብር ተግባር መፈጸምም የድርጅቶቹ ጠቅላላ መገለጫ በመሆኑ፤ ድርጅቶቹ በሽብርተኛ ድርጅትነት እንዲሰየሙ ነው የውሳኔ ሐሳብ የተላለፈው።

ተዛማጅ ጽሑፍ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

ትኩስ ርዕስ

- Advertisment -spot_img