አምባ ዲጂታል፤ ዐርብ ሐምሌ 8፣ 2014 ― ያለ መከሰስ መብታቸው እንዲነሳ የተጠየቀው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባል ዶክተር ሙሉቀን ሐፍቱ ናቸው፡፡
የምክር ቤት አባሉ ያለ መከሰስ መብት እንዲነሳ የተጠየቀው ባለፈው ሳምንት ከወጣው የአዲስ አበባ ከተማ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ጋር በተገናኘ ነው፡፡
የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት መረጃ እንዳመለከተው የከተማ አስተዳደሩ የሕግ ከለላው ይነሳልን ጥያቄውን ለፍትሕ ሚኒስቴር ያቀረበው ግለሰቡ ከቤቶች እጣ አወጣጥ ጋር በተያያዘ እና የተሰጣቸውን ስልጣንና ሃላፊነት በአግባቡ ባለመጠቀም በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለው እንዲጣራ ለማድረግ ነው፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካወጣው የጋራ መኖሪያ ቤቶች እጣ ጋር በተገናኘ ተፈጽሟል ባለው መጭበርበር አሁን ያለ መከሰሰስ መብታቸው ይነሳልኝ ካላቸው ዶክተር ሙለቀን ሐፍቱ በተጨማሪ ሌሎች 10 ባለሞያዎችና ኃላፊዎችን በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ማድረጉ ይታወቃል፡፡
የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ረቡዕ ሐምሌ 6 በሰጡት መግለጫ በተፈጸመው የማጭበርበር ተግባር ምክንያት የወጣው ዕጣ እንዲሰረዝ መደረጉን አስታውቀዋል፡፡
[…] The Addis Ababa city administration has dismissed the recent condominium lottery draw due to a claimed tech tampering by officials within the city administration. It also announced that it is inquiring into the case and investigating the officials. […]
[…] ዕጣ በአስተዳደሩ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች እና አንዳንድ ባለስልጣናት በዕጣው የማጭበርበር ሂደት ውስጥ ተሳትፈዋል በማለት የእጣ […]